መስቀል እና ሠላጢን እንዴትና መቸ በማን እንደ ተጋጠሙ እቅጩን ማወቅ ያዳግታል። ሁለቱ የሚያበስሩት ፍልስፍና ግን የተድበሰበሰ ነገር የለውም። ወይ ሰላም ወይ ፀብ። ሰላም እና ፀብ። በሰላም ከመጣ አሳልመው፤ በፀብ ከመጣ ጎኑን ወግተህ ጣለው… ከጅምሩ የጠበኛና የጠርጣራ ሰው ሥራ ይመስላል፤ ጨርሶ…
መሪነት፣ የነገሮችን አካሄድና ፍጻሜ ከጅምሩ ለተለሙ ነው። መሪነት፣ ዐይናቸውን ከግባቸው ላይ ሳያነሡ በየእርከኑ ሁኔታን ለሚያቃኑ ነው። መሪነት፣ ምሥጋናን ለሚጋሩ ነው። መሪነት፣ ውርደት ውርደቱን ማንም እንደማይጋራቸው ለተገነዘቡ ነው። የመሪዎች አበሳ የሚጀምረው ዓላማቸውን ግልጽ ሳያደርጉ ሲቀር፣ ዓላማቸውን እንደየሁኔታው ደጋግመው ሳያጠሩ ሲቀር፣ ተቀናቃኞች…
ወደ አንድ መንደር መጣ። ከፊት ለፊቱ የሚታየውን ቤት ሄዶ አንኳኳ። ደጋግሞ አንኳኳ፤ የሰውም የውሻም ድምጽ አልተሰማም። አልከፈቱለትም። አለፍ ብሎ ሌላ ደጅ አንኳኳ። ማ ልበል? አሉ። ማ ልበል? ብለው ወሬአቸውን ቀጠሉ እንጂ ተነሥተው አልከፈቱለትም። ወረድ ብሎ አንኳኳ። ሲከፍቱለት ተገትሮ ቆሟል። ቊመናውን…
ፕሮፌሰር መስፍን “ኑዛዜ” በተሰኘ ግጥም ያልተጠበቀ ጥያቄ ትተውልን አልፈዋል። ኑዛዜአቸውን ይፋ ያደረጉት ሰኔ 2005 ዓ.ም. በ “የሚወለዱበት… መሬት” ጽሑፋቸው ነው። “በራሴ በኩል አውጥቼ አውርጄ ውሳኔ ላይ ከደረስሁ ቆይቻለሁ፤ መቀበር አልፈልግም… ለህልፈት ስበቃ የሬሳን ፈቃድ የሚፈጽም ከተገኘ… አቃጥሉልኝ ሬሣዬን..” ብለዋል። ኑዛዜአቸው…
ከእለታት አንድ ቀን የአካል ክፍሎች አደሙ፤ በሆድ ላይ አደሙ። እኛ በደከምንበት ምንም ሳይሠራ ሆድ ለምን ቊጭ ብሎ ይበላል ብለው አደሙ፤ ዝግ ስብሰባ ጠሩ። እጅ ተናገረ፦ ያረስኩ እኔ፣ ያረምኩ እኔ፣ የወቃሁ እኔ፣ ያበሰልኩ እኔ … ዐይን አቋረጠውና በምንህ አይተህ? አለ። መብሰሉን…
በር መሸጋገሪያ ነው፤ ከአዲስ ወደ አሮጌ መሻገሪያ፤ ከአሮጌ ወደ አዲስ መሻገሪያ። ከሞት ወደ ሕይወት። ከሠፈር ወደ ሌላ ሠፈር። ከዛሬ ወደ ነገ። ከሹመት ወደ ሽረት፤ ከሽረት ወደ ሹመት። ሽግግሩ አንዳንዴ በምርጫ ነው፣ አንዳንዴ ያለምርጫ። መወለድና ሞት በምርጫ ነው? ተሻግሮ ከበር ወዲያ…
In the tradition of Eastern and Western patriotic and pastoral poets (Elisheva Bikhovski, Darwish, Frost, Bejan Matur, Tagore, and Tennyson) poet-playwright Tsegaye Gabre-Medhin’s seminal work እሳት ወይ አበባ Esat woy Ababa Blaze or Bloom (2007) is replete with references to…